Warning: mkdir(): No space left on device in /var/www/tg-me/post.php on line 37

Warning: file_put_contents(aCache/aDaily/post/orthodox1/--): Failed to open stream: No such file or directory in /var/www/tg-me/post.php on line 50
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 | Telegram Webview: orthodox1/13232 -
Telegram Group & Telegram Channel
#ጾም_በክርስትና_ሕይወት

በዚህ ትምህርታዊ ጹሑፍ ስለ ጾም አራት ነጥቦችን እናያለን
1.የጾም ትርጉም
2.ጾም ያስፈለገበት ምክንያት
3.የጾም ጥቅሞች
4.በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን፡፡
ከላይ ከ1-4 ተራ ቊጥር የተገለጹትን እንደሚከተለው በዝርዝር እናያለን፡፡

1ኛ/ የጾም ትርጉም
ጾም፡- ማለት ክርስቲያን የሆነ ሰው ሁሉ ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ከእህል ከውኃ ተከልክሎ መቆየት ማለት ሲሆን ከሥጋ፣ ከቅቤና፣ ከእንቁላል ደግሞ እንድንጾምባቸው የተወሰኑ የአጽዋማት ሳምንታት እስኪጠናቀቁ የምንከለከልበት ማለት ነው፡፡ /ፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 15/
ከዚህም ጋር ጾም ማለት፡- ዓይን ክፉ ከማየት ጆሮ ክፉ ከመስማት፣ አንደበት ክፉ ከመናገር፣ እጅ ክፉ ከመሥራት በአጠቃላይ ሰውነት የኃጢአት ሥራ ከመሥራት የሚገታበት፣ የሚከለከልበት ማለት ነው፡፡ /ቅዱስ ያሬድ/

ጾም፡- ሁለት ዓይነት ነው ይኸውም
ሀ. የአዋጅ ጾም ነው፡- ይህም በስውር ሳይሆን ሁሉ አውቆት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ይህም መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት አለው፡፡ “በጽዮን መለከትን ንፉ ጾምንም ቀድሱ ጉባኤውንም አውጁ” /ኢዩ. 2፡15/
ሰባቱ አጽዋማት የአዋጅ ጾሞች ናቸው፡፡ እነዚህም እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡
1. የነቢያት ጾም
2. የገሀድ ጾም
3. የነነዌ ጾም
4. ዐቢይ ጾም
5. የሐዋርያት ጾም
6. ጾመ ድኅነት /ረቡዕና ዓርብ/
7.ጾመ ፍልሰታ
ለ. የግል ጾም ነው፡- የግል ጾም ስንል አንድ ሰው በሠራው ኃጢአት ምክንያት ለንስሓ አባቱ ተናግሮ የሚሰጠው የንስሓ ጾም ሲሆን እንዲሁም አንድ ሰው ስለደረሰበትና በእርሱ ላይ ስለሆነ ነገር ስለሚፈልገው ጉዳይ እግዚአብሔር ተገቢውን መልስ እንዲሰጠው የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ዳዊት ልጁ በታመመ ጊዜ ጹሟል፡፡ /2ኛ.ሳሙ. 12፡16/
ነገር ግን በግል ጾም ጊዜ ጾሙ ይፋ ስላልሆነ ራስን መሰወር እንደሚያስፈልግ ታዟል፡፡
ይህንንም አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ “ስትጾሙም እንደ ግብዞች አትጠውልጉ ለሰዎች ሊታዩ እንደ ጾመኛ ፊታቸውን ያጠወልጋሉና አንተ ግን ስትጾም ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ በስውር የሚያይህ አባትህ በግልጥ ይከፍልሃል” /ማቴ. 6፡16-18/ ይህ ቅዱስ ቃል ስለግል ጾም የተነገረ ነው፡፡ በዚህ መሠረት የግል ጾምን ከጿሚው ሰው እና ከእግዚአብሔር ውጭ ማንም ማወቅ የለበትም፡፡

2ኛ/ ጾም ያስፈለገበት ምክንያት
ጾም፡- ያስፈለገበት ምክንያት ልጓመ ሥጋ ስለሆነ ነው፡፡ ሰው ሁልጊዜ የጣመ የላመ ምግብ የማይለየውና እንደልቡ እየበላ እየጠጣ ሳይጾም የሚኖር ከሆነ ለኃጢአት ይጋለጣል፡፡ ይህም በፍትሐ ነገሥት ተጽፏል፡፡ “ከመ ያድክም ኃይለ ፍትወት” (ኃይለ ፍትወትን፣ ሥጋዊ ፍትወትን ያደክም ዘንድ ጾም ታዘዘ) /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/ እንዲሁም በምንጾምበት ጊዜ ረሀብን፣ ችግርን እናውቃለን፡፡ “ከመ ያእምር ጸዋሚ ሕማመ ረኀብ ወይምሐሮሙ ለርኁባን” (ጿሚ ሰው የረኀብን ችግር ያውቅ ዘንድና ለተራቡ ይራራ ዘንድ ጾም ታዘዘ) /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/ እንዲሁም “ችግርን የቀመሰ ችግርን ያውቃል” እንዲሉ አባቶቻችን፡፡

3ኛ/ የጾም ጥቅሞች
የጾም ጥቅሞች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡
1.በጾም መንግሥተ ሰማያትን እንወርሳለን፡፡
ይህንንም የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ “ስለጽድቅ ብለው የሚራቡና የሚጠሙ ንዑዳን ክቡራን ናቸው እነርሱ ይጠግባሉና” /ማቴ. 5፡6/ ሲል ተናግሯል፡፡
2.በጾም በአገር ላይ የታዘዘው መቅሠፍት ይርቃል፡፡
የነነዌ ሰዎች የዮናስን ትምህርት መሠረት በማድረግ ሦስት ቀን ጾሙ፡፡ ለእነርሱ የታዘዘው እሳት የዛፉን ጫፍ ጫፍ አቃጥሎ ተመልሷል፡፡ /ትን ዮናስ ም. 3 በሙሉ/

3.በጾም ሰይጣን ድል ይሆናል፡፡
“እንዲህ ዓይነት አብሮ አደግ ጋኔን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም” /ማቴ. 17፡21/ ሲል ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌል የተናገረው ቃል ሰይጣን በጾም ድል እንደሚሆን የሚገልጽ ነው፡፡
4.ጾም ከፈተና፣ ከመከራ ያድናል፡፡
ነቢዩ ዳንኤል በጾም ከአፈ አናብስት (ከአንበሶች አፍ) ድኗል፡፡ /ትን. ዳን. ም. 6 በሙሉ/ ሶስና በጾም ከሐሰት ምስክሮች ድናለች፡፡ /መጽ. ሶስና ም. 1 ሙሉ/ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም ከፈተና፣ ከመከራ ድነዋል፡፡
5.ጾም ዕድሜን ያረዝማል፡፡
ጾም የመልካም ሥራ ሁሉ መሠረት በመሆኑ ዕድሜን ያረዝማል፡፡
ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በገድላቸው እንደተጻፈው ዕድሜልካቸውን በጾም ነው የኖሩት የእናታቸውን ጡት እንኳን አልጠቡም፡፡ በዚህ ዓለም የኖሩት አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ዓመት ነው፡፡ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም የዕድሜ ባለጸጎች ሆነዋል፡፡
6.በጾም ምስጢር ይገለጻል፡፡
አይሁድ አርባ ስድስቱን መጻሕፍተ ብሉያት ቆነጻጽለው ባጠፏቸው ጊዜ ዕዝራ ሱቱኤል አዝኖ አርባ ቀን ጾመ ከዚህ በኋላ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ሰማያዊ መጠጥ በብርሃን ጽዋ (ጽዋዓ እሳት) ለዕዝራ አጠጣው ዕዝራም ምስጢር ተገልጾለት አርባ ስድስቱን መጻሕፍተ ብሉያት ጽፏል፡፡ /መጽ. ዕዝ. ሱቱ. 13፡36-41/ ሌሎችም ደጋግ ሰዎች በጾም ምስጢር ተገልጾላቸዋል፡፡
7.በጾም ኃጢአት ይሠረያል፡፡
የነነዌ ሰዎች የዮናስን ትምህርት መሠረት በማድረግ ሦስት ቀን ጾመው ኃጢአታቸው ተሠርዮላቸዋል፡፡ /ትን. ዮናስ ም. 3 በሙሉ/ ሌሎችም ሰዎች በጾም ኃጢአታቸው ተሠርዮላቸዋል፡፡ ይህንንም ታላቁ ሊቅ መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ያሬድ በዜማ ድርሰቱ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ “በጾም ወበጸሎት ይሠረይ ኃጢአት” (በጾምና በጸሎት ኃጢአት ይሠረያል)
8.በጾም ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ይቻላል፡፡
ሊቀ ነቢያት ሙሴ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሞ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል በቃል ተነጋግሯል፡፡ /ዘዳግም. 9፡9-14/
ነቢዩ ኤልያስም በጾም ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋግሯል፡፡ /1ኛ. መጽ. ነገ. 17፡2/
9.በጾም ልመናችን ይፈጸማል፡፡
እስራኤል በጾም የለመኑትን አግኝተዋል፡፡ /1ኛ ሳሙ. 7፡6-14/ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም ልመናቸው ተፈጽሞላቸዋል፡፡
የጾም ጥቅሞች ከላይ ከ1-9 ተራ ቊጥር የተገለጹ ሲሆን ከላይ በርእሱ እንደተገለጸው ጾም የመልካም ሥራ ሁሉ መሠረት ሲሆን በአንጻሩ አለመጾም ደግሞ የኃጢአት ሁሉ መሠረት ነው፡፡ ምክንያቱም ሰው ካልጾመ ለብዙ ኃጢአት ይጋለጣል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ ለሰዎች የተሰጠው የጾም ትእዛዝ ነው፡፡ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን፡- ይህን ዕፀ በለስ አትብሉ ሲል ከዕፀ በለሱ ተከልከሉ ጹሙ ማለቱ ነው፡፡ እነርሱ ግን አትብሉ የተባሉትን በሉ ከገነት ወጡ ተጎዱ አለመጾም ያስጎዳል፡፡ በዚህ መሠረት ኃጢአት በመብል ምክንያት ወደዓለም ገባ፡፡

4ኛ/ በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
ጾም፡- ከትርጉሙ እንደተረዳነው ከእህል ከውኃ ከመከልከሉ ጋር ከክፉ ነገር ከኃጢአት መራቅ ስለሆነ ጾማችን ከክፉ ነገር በመራቅ፣ በቅን ልቡና፣ በንጹሕ ልብ መሆን አለበት፡፡ እንዲሁም ነቢዩ ኢሳይያስ “በምትጾምበት ጊዜ እንጀራህን ለተራበ ብትቆርስ ብርሃንህ እንደንጋት ይበራል የዚያን ጊዜ ትጠራለህ እግዚአብሔርም ይሰማሃል ትጮሀለህ እርሱም እነሆ ይልሃል” /ኢሳ. 58፡6-9/ ባለው መሠረት በጾም ጊዜ የጧት ቁርሳችን ለድሆች ከተሰጠ ሰማያዊ ዋጋ እናገኛለን፡፡



tg-me.com/orthodox1/13232
Create:
Last Update:

#ጾም_በክርስትና_ሕይወት

በዚህ ትምህርታዊ ጹሑፍ ስለ ጾም አራት ነጥቦችን እናያለን
1.የጾም ትርጉም
2.ጾም ያስፈለገበት ምክንያት
3.የጾም ጥቅሞች
4.በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን፡፡
ከላይ ከ1-4 ተራ ቊጥር የተገለጹትን እንደሚከተለው በዝርዝር እናያለን፡፡

1ኛ/ የጾም ትርጉም
ጾም፡- ማለት ክርስቲያን የሆነ ሰው ሁሉ ለተወሰነ ጊዜና ሰዓት ከእህል ከውኃ ተከልክሎ መቆየት ማለት ሲሆን ከሥጋ፣ ከቅቤና፣ ከእንቁላል ደግሞ እንድንጾምባቸው የተወሰኑ የአጽዋማት ሳምንታት እስኪጠናቀቁ የምንከለከልበት ማለት ነው፡፡ /ፍትሕ መንፈሳዊ አንቀጽ 15/
ከዚህም ጋር ጾም ማለት፡- ዓይን ክፉ ከማየት ጆሮ ክፉ ከመስማት፣ አንደበት ክፉ ከመናገር፣ እጅ ክፉ ከመሥራት በአጠቃላይ ሰውነት የኃጢአት ሥራ ከመሥራት የሚገታበት፣ የሚከለከልበት ማለት ነው፡፡ /ቅዱስ ያሬድ/

ጾም፡- ሁለት ዓይነት ነው ይኸውም
ሀ. የአዋጅ ጾም ነው፡- ይህም በስውር ሳይሆን ሁሉ አውቆት ክርስቲያን የሆነ ሁሉ የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ይህም መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረት አለው፡፡ “በጽዮን መለከትን ንፉ ጾምንም ቀድሱ ጉባኤውንም አውጁ” /ኢዩ. 2፡15/
ሰባቱ አጽዋማት የአዋጅ ጾሞች ናቸው፡፡ እነዚህም እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡
1. የነቢያት ጾም
2. የገሀድ ጾም
3. የነነዌ ጾም
4. ዐቢይ ጾም
5. የሐዋርያት ጾም
6. ጾመ ድኅነት /ረቡዕና ዓርብ/
7.ጾመ ፍልሰታ
ለ. የግል ጾም ነው፡- የግል ጾም ስንል አንድ ሰው በሠራው ኃጢአት ምክንያት ለንስሓ አባቱ ተናግሮ የሚሰጠው የንስሓ ጾም ሲሆን እንዲሁም አንድ ሰው ስለደረሰበትና በእርሱ ላይ ስለሆነ ነገር ስለሚፈልገው ጉዳይ እግዚአብሔር ተገቢውን መልስ እንዲሰጠው የሚጾመው ጾም ነው፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ዳዊት ልጁ በታመመ ጊዜ ጹሟል፡፡ /2ኛ.ሳሙ. 12፡16/
ነገር ግን በግል ጾም ጊዜ ጾሙ ይፋ ስላልሆነ ራስን መሰወር እንደሚያስፈልግ ታዟል፡፡
ይህንንም አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ “ስትጾሙም እንደ ግብዞች አትጠውልጉ ለሰዎች ሊታዩ እንደ ጾመኛ ፊታቸውን ያጠወልጋሉና አንተ ግን ስትጾም ለሰዎች እንዳትታይ ራስህን ተቀባ በስውር የሚያይህ አባትህ በግልጥ ይከፍልሃል” /ማቴ. 6፡16-18/ ይህ ቅዱስ ቃል ስለግል ጾም የተነገረ ነው፡፡ በዚህ መሠረት የግል ጾምን ከጿሚው ሰው እና ከእግዚአብሔር ውጭ ማንም ማወቅ የለበትም፡፡

2ኛ/ ጾም ያስፈለገበት ምክንያት
ጾም፡- ያስፈለገበት ምክንያት ልጓመ ሥጋ ስለሆነ ነው፡፡ ሰው ሁልጊዜ የጣመ የላመ ምግብ የማይለየውና እንደልቡ እየበላ እየጠጣ ሳይጾም የሚኖር ከሆነ ለኃጢአት ይጋለጣል፡፡ ይህም በፍትሐ ነገሥት ተጽፏል፡፡ “ከመ ያድክም ኃይለ ፍትወት” (ኃይለ ፍትወትን፣ ሥጋዊ ፍትወትን ያደክም ዘንድ ጾም ታዘዘ) /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/ እንዲሁም በምንጾምበት ጊዜ ረሀብን፣ ችግርን እናውቃለን፡፡ “ከመ ያእምር ጸዋሚ ሕማመ ረኀብ ወይምሐሮሙ ለርኁባን” (ጿሚ ሰው የረኀብን ችግር ያውቅ ዘንድና ለተራቡ ይራራ ዘንድ ጾም ታዘዘ) /ፍትሐ ነገሥት አንቀጽ 15/ እንዲሁም “ችግርን የቀመሰ ችግርን ያውቃል” እንዲሉ አባቶቻችን፡፡

3ኛ/ የጾም ጥቅሞች
የጾም ጥቅሞች እንደሚከተለው ተዘርዝረዋል፡፡
1.በጾም መንግሥተ ሰማያትን እንወርሳለን፡፡
ይህንንም የሰላም አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ “ስለጽድቅ ብለው የሚራቡና የሚጠሙ ንዑዳን ክቡራን ናቸው እነርሱ ይጠግባሉና” /ማቴ. 5፡6/ ሲል ተናግሯል፡፡
2.በጾም በአገር ላይ የታዘዘው መቅሠፍት ይርቃል፡፡
የነነዌ ሰዎች የዮናስን ትምህርት መሠረት በማድረግ ሦስት ቀን ጾሙ፡፡ ለእነርሱ የታዘዘው እሳት የዛፉን ጫፍ ጫፍ አቃጥሎ ተመልሷል፡፡ /ትን ዮናስ ም. 3 በሙሉ/

3.በጾም ሰይጣን ድል ይሆናል፡፡
“እንዲህ ዓይነት አብሮ አደግ ጋኔን ያለ ጾምና ጸሎት አይወጣም” /ማቴ. 17፡21/ ሲል ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በቅዱስ ወንጌል የተናገረው ቃል ሰይጣን በጾም ድል እንደሚሆን የሚገልጽ ነው፡፡
4.ጾም ከፈተና፣ ከመከራ ያድናል፡፡
ነቢዩ ዳንኤል በጾም ከአፈ አናብስት (ከአንበሶች አፍ) ድኗል፡፡ /ትን. ዳን. ም. 6 በሙሉ/ ሶስና በጾም ከሐሰት ምስክሮች ድናለች፡፡ /መጽ. ሶስና ም. 1 ሙሉ/ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም ከፈተና፣ ከመከራ ድነዋል፡፡
5.ጾም ዕድሜን ያረዝማል፡፡
ጾም የመልካም ሥራ ሁሉ መሠረት በመሆኑ ዕድሜን ያረዝማል፡፡
ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በገድላቸው እንደተጻፈው ዕድሜልካቸውን በጾም ነው የኖሩት የእናታቸውን ጡት እንኳን አልጠቡም፡፡ በዚህ ዓለም የኖሩት አምስት መቶ ስልሳ ሁለት ዓመት ነው፡፡ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም የዕድሜ ባለጸጎች ሆነዋል፡፡
6.በጾም ምስጢር ይገለጻል፡፡
አይሁድ አርባ ስድስቱን መጻሕፍተ ብሉያት ቆነጻጽለው ባጠፏቸው ጊዜ ዕዝራ ሱቱኤል አዝኖ አርባ ቀን ጾመ ከዚህ በኋላ ታላቁ መልአክ ቅዱስ ዑራኤል ሰማያዊ መጠጥ በብርሃን ጽዋ (ጽዋዓ እሳት) ለዕዝራ አጠጣው ዕዝራም ምስጢር ተገልጾለት አርባ ስድስቱን መጻሕፍተ ብሉያት ጽፏል፡፡ /መጽ. ዕዝ. ሱቱ. 13፡36-41/ ሌሎችም ደጋግ ሰዎች በጾም ምስጢር ተገልጾላቸዋል፡፡
7.በጾም ኃጢአት ይሠረያል፡፡
የነነዌ ሰዎች የዮናስን ትምህርት መሠረት በማድረግ ሦስት ቀን ጾመው ኃጢአታቸው ተሠርዮላቸዋል፡፡ /ትን. ዮናስ ም. 3 በሙሉ/ ሌሎችም ሰዎች በጾም ኃጢአታቸው ተሠርዮላቸዋል፡፡ ይህንንም ታላቁ ሊቅ መሠረተ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ያሬድ በዜማ ድርሰቱ እንዲህ ሲል ተናግሯል፡፡ “በጾም ወበጸሎት ይሠረይ ኃጢአት” (በጾምና በጸሎት ኃጢአት ይሠረያል)
8.በጾም ከእግዚአብሔር ጋር መነጋገር ይቻላል፡፡
ሊቀ ነቢያት ሙሴ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾሞ ከእግዚአብሔር ጋር ቃል በቃል ተነጋግሯል፡፡ /ዘዳግም. 9፡9-14/
ነቢዩ ኤልያስም በጾም ከእግዚአብሔር ጋር ተነጋግሯል፡፡ /1ኛ. መጽ. ነገ. 17፡2/
9.በጾም ልመናችን ይፈጸማል፡፡
እስራኤል በጾም የለመኑትን አግኝተዋል፡፡ /1ኛ ሳሙ. 7፡6-14/ ሌሎችም ቅዱሳን በጾም ልመናቸው ተፈጽሞላቸዋል፡፡
የጾም ጥቅሞች ከላይ ከ1-9 ተራ ቊጥር የተገለጹ ሲሆን ከላይ በርእሱ እንደተገለጸው ጾም የመልካም ሥራ ሁሉ መሠረት ሲሆን በአንጻሩ አለመጾም ደግሞ የኃጢአት ሁሉ መሠረት ነው፡፡ ምክንያቱም ሰው ካልጾመ ለብዙ ኃጢአት ይጋለጣል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ ለሰዎች የተሰጠው የጾም ትእዛዝ ነው፡፡ አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር አዳምና ሔዋንን፡- ይህን ዕፀ በለስ አትብሉ ሲል ከዕፀ በለሱ ተከልከሉ ጹሙ ማለቱ ነው፡፡ እነርሱ ግን አትብሉ የተባሉትን በሉ ከገነት ወጡ ተጎዱ አለመጾም ያስጎዳል፡፡ በዚህ መሠረት ኃጢአት በመብል ምክንያት ወደዓለም ገባ፡፡

4ኛ/ በምን ዓይነት መንገድ መጾም እንዳለብን እንደሚከተለው ተገልጿል፡፡
ጾም፡- ከትርጉሙ እንደተረዳነው ከእህል ከውኃ ከመከልከሉ ጋር ከክፉ ነገር ከኃጢአት መራቅ ስለሆነ ጾማችን ከክፉ ነገር በመራቅ፣ በቅን ልቡና፣ በንጹሕ ልብ መሆን አለበት፡፡ እንዲሁም ነቢዩ ኢሳይያስ “በምትጾምበት ጊዜ እንጀራህን ለተራበ ብትቆርስ ብርሃንህ እንደንጋት ይበራል የዚያን ጊዜ ትጠራለህ እግዚአብሔርም ይሰማሃል ትጮሀለህ እርሱም እነሆ ይልሃል” /ኢሳ. 58፡6-9/ ባለው መሠረት በጾም ጊዜ የጧት ቁርሳችን ለድሆች ከተሰጠ ሰማያዊ ዋጋ እናገኛለን፡፡

BY ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/orthodox1/13232

View MORE
Open in Telegram


ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Export WhatsApp stickers to Telegram on iPhone

You can’t. What you can do, though, is use WhatsApp’s and Telegram’s web platforms to transfer stickers. It’s easy, but might take a while.Open WhatsApp in your browser, find a sticker you like in a chat, and right-click on it to save it as an image. The file won’t be a picture, though—it’s a webpage and will have a .webp extension. Don’t be scared, this is the way. Repeat this step to save as many stickers as you want.Then, open Telegram in your browser and go into your Saved messages chat. Just as you’d share a file with a friend, click the Share file button on the bottom left of the chat window (it looks like a dog-eared paper), and select the .webp files you downloaded. Click Open and you’ll see your stickers in your Saved messages chat. This is now your sticker depository. To use them, forward them as you would a message from one chat to the other: by clicking or long-pressing on the sticker, and then choosing Forward.

Tata Power whose core business is to generate, transmit and distribute electricity has made no money to investors in the last one decade. That is a big blunder considering it is one of the largest power generation companies in the country. One of the reasons is the company's huge debt levels which stood at ₹43,559 crore at the end of March 2021 compared to the company’s market capitalisation of ₹44,447 crore.

ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴 from ms


Telegram ኦርቶዶክስ ተዋህዶ - ‌🇴‌🇷‌🇹‌🇭‌🇴‌🇩‌🇴‌🇽 ‌🇹‌🇪‌🇼‌🇦‌🇭‌🇩‌🇴
FROM USA